ኢራን በዛሬው ዕለት በሰሜናዊ እስራኤል ባስወነጨፈቻቸው ሚሳኤሎች በርካቶች መጎዳታቸው ተነገረ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ኢራን በዛሬው ዕለት በሰሜናዊ እስራኤል ባስወነጨፈቻቸው ሚሳኤሎች በርካቶች መጎዳታቸውን የአገሪቱ የአደጋ ጊዜ አገልግሎት አስታወቀ።
የ40 ዓመት ወንድ፣ የ16 ዓመት ወንድ እና የ54 ዓመት ግለሰብ በጠና መቁሰላቸውን የእስራኤል የአደጋ ጊዜ አገልግሎት ማገን ዴቪድ አዶም ገልጿል።
ሌሎች 20 የሚሆኑት ደግሞ በመለስተኛ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን እና ብዙዎቹም በፍንዳታ እና በፍንጣሪዎች ቆስለዋል ብሏል።
በካርሚኤል መጠለያ የነበረች አንዲት የ51 ዓመት ግለሰብ በልብ ድካም ህይወቷ ማለፉ ተገልጿል።























